![](https://evangelische-beratung.com/am/wp-content/uploads/sites/9/2019/08/Schuldnerberatung_HERO-1024x401.jpg)
ይህንን ያዉቃሉ ?
- ምን ያህል (ብድር) እንዳለብዎት ለመገመት አልቻሉም ?
- በፖስታ ሣጥንዎ ዉስጥ የማስጠንቀቂያ ደብዳቤዎችና ከፍርድ ቤት ታዘዉ በግዳጅ እዳ የሚያስከፍሉ ሠዎች የቀጠሮ ደብዳቤዎችን ነዉ ወይ የሚያገኙት ?
- ደሞዝዎ ወይም የባንክ ሂሳብዎ እንዳያንቀሳቅሱ ታግድብዎታል፣ ከባንክ ገንዘብ ማዉጥት አይችሉም ?
- ያለዎት ገንዘብዎ ለምንም በቂ አይደለም ?
እርስዎ አሁን ይህንን ሁኔታ መለወጥ ይፈልጋሉ ?
እኛ በሚከተሉት ጉዳዮች እንረዳዎታለን
- አደገኛና አስቸኳይ ችግር ላይ ከወደቁ
- እርስዎ ያሉበትን ሁኔታ ወይም ችግሮችዎን በትክክል ለመረዳት ከፈለጉ
- ከባለ እዳዎችዎ ጋር ያለዉን ግኑኝነት ጤናማ ለማድረግ ከፈለጉ
- ስለ ታገደብዎት የባንክ ሂሳብ ጥያቄዎች ካሉዎት፣ ከታገደብዎት የባንክ ሂሳብ እገዳዉም ቢኖር ለማዉጣት ከተፈቀደልዎት መጠን በላይ ተጨማሪ ምን ያህል ማዉጣት እንደሚቻል ማወቅ ከፈለጉ
- ያለብዎትን እዳዎች ለመክፈል ያለዎት ንብረት በኪሳራ ምክንያት በግዴታ ለጨረታ ይቅረብ ቢባልም ባይባልም እንዴት ችግሩን ማስተካከል እንድሚቻል ማወቅ ከፈለጉ
እኛ እዳን በተመለከተ / ኪሣራን በተመለከተ አንቀጽ 305 የኪሣራ ደንብ (§ 305 Insolvenzordnung) በሚደነግገዉ መሠረት በኦፍንባህ ከተማ (Offenbach) በሕግ እዉቅና ያለን አማካሪዎች ነን ።
እርስዎ የሚኖሩት በኦፍንባህ (Offenbach) ነዉ ? ታዲያ ወደ እኝ ይምጡ !
Evangelisches Zentrum für Beratung in Offenbach
069 / 829 770 40
Arthur Zitscher Straße 13
63065 Offenbach
Offene Sprechstunden:
Montags 15.00 Uhr – 17.30 Uhr
Mittwochs 09.00 Uhr – 11.30 Uhr
Freitags 09.00 Uhr – 11.30 Uhr
![](https://evangelische-beratung.com/am/wp-content/uploads/sites/9/2019/08/Zentrum-Offenbach-1-1024x684.jpg)
Ihre Ansprechpartner*innen im Evangelischen Zentrum für Beratung in Offenbach
![](https://evangelische-beratung.com/wp-content/uploads/2019/08/ernst-bruenner_schuldnerberatung-e1576419080456-300x290.jpg)
![](https://evangelische-beratung.com/am/wp-content/uploads/sites/9/2019/08/Michael-Franke_Leitung-Offenbach-300x200.jpg)
![](https://evangelische-beratung.com/wp-content/uploads/2020/01/portrait_platzhalter-1-300x300.jpg)
![](https://evangelische-beratung.com/wp-content/uploads/2020/01/portrait_platzhalter-1-300x300.jpg)
የምክር አገልግሎቱ ከሃይማኖት፣ ከግል አመለካከት ና ከብሔረሰብ ማንነት ነጻ የሆነ ነዉ። እኛ ሚስጢራዊ፣ ከጥገኝነትና ከክፊያ ነጻ የሆነ ምክር እንሰጥዎታለን።
እርስዎ የሚኖሩት በፍራንክፌርት (Frankfurt) ከተማ ነዉ ?
ከሆነ እባክዎን ከታች ያለዉን ይመልከቱ :
የእዳ ምክር አገልግሎት በሌሎቸ ቦታዎች :
የመጀመሪያ መረጃዎችን እዚህ ያገኛሉ: